ትምህርተ ኃይማኖት_005

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት


አምስቱ አእማደ ምሥጢር

1. ምሥጢረ ሥላሴ
2. ምሥጢረ ሥጋዌ
3. ምሥጢረ ጥምቀት
4. ምሥጢረ ቁርባን
5. ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን
 
1. ምሥጢረ ሥላሴ
ሠለሰ ሶስት አደረገ ፤ ካለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ፤ ሥላሴ ማለት ሶስትነት ማለት ነው ። በዚህ ትምህርት የአምላክን አንድነት ሶስትነት እንማራለን ።
የምሥጢረ ሥላሴን ትምህርት በምንማርበት ጊዜ ከሂሳብ ቀመር ህግ አስተሳሰብ ውጭ ሆነን ነው ። ምክንያቱም መንሳዊዉ ሥጋዊዉን ጥበብ (ፍልስፍና) ይመረምረዋል እንጅ መንፈሳዊ ጥበብና ምሥጢር በዓለማዊ ዕውቀት ምርምር ሊደረስበት አይቻልምና ። የሃይማኖት ነገር ቁሳዊ ሳይሆን መንፈሳዊና በሃይማኖት ሆኖ በመንፈሳዊነት የሚታወቅና የሚታመ ን ነው ።
የምሥጢረ ሥላሴ ትምህርት በብሉይ ኪዳን
ዘፍ 1 ፥ 26 ። “ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር አለ” ። ከዚህ ቃል በፊት እግዚአብሔርን የሚመስል ፍጡር መኖሩን የሚገልጽ ባለመኖሩ “በመልካችን…”የሚለው እግዚአብሔር የራሱ የሆነ ከአንድ በላይ መልክ እንዳለው ያስረዳል ። እግዚአብሔር ዓለምን ሲፈጥር ማንም እንዳላማከረውና ረዳትም እንዳላስፈለገው በኢሳ 40 ፥ 12 ። ላይ ተጽፎ እናገኛለን ። በመ ሆኑም “በመልካችን..”የሚለው ሶስትነቱን(ከአንድ በላይ መሆኑን)“አለ” የሚለው ደግሞ አንድነቱን ይገልጽልናል ።
“አዳም ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ” ዘፍ 3 ፥ 22 ። እግዚአብሔር በአካልና በስምና በግብር ሶስትነት ባይኖረው ኖሮ “እንደ እኔ ሆነ” በማለት ይናገር ነበር ። “ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ” የሚለው ግን ብዙ ቁጥርን አመላካች በመሆኑ እግዚአብሔር አንድ ብቻ እንዳልሆነ ያስረዳናል ።
ዘፍ 11 ፥ 7 ። “ኑ እንውረድና ቋንቋቸውን እንደባልቀው አለ” ይህ ቃል አንዱ ሌሎቹን ኑ እንደሚል እንረዳለን ። በዚህም እግዚአብሔር ለአምላክነት ሥራው የማንንም እርዳታ እንደማይፈልግ የሚታወቅ ሲሆን በውስጡ ከሁለት በላይ እንደሆነ አንዱ ሌሎቹን “ኑ” በማለቱ ያስረዳል ።
ዘፍ 18 ፥ 1 ። እግዚአብሔር በመምሬ ዛፍ ስር ለአብርሐም ተገለጠለት ። አብርሐምም ዓይኑን አነሳና ሶስት ሰዎችን አየ የሚለው እግዚአብሔር በሶስትነቱ በሰዎች አምሳል ለአብርሐም መገለጡን በቁጥር ሶሰት ብሎ ያስረዳል ። ሀሳቡን ግልጽ ለማድረግ እግዚአብሔር ከሶስት ሰዎች ጋር ወይም ከሁለት መላእክት ጋር ተገለጠለት አይልም ። መላእክትም ሆኑ ሰዎች በዚህ ሥም አይጠሩም ኢሳ 42 ፥ 8 ። እስከዚህ ድረስ ብዛትን ብቻ ሲያመልክት የነበረው በዚህ ላይ ሶስት ብሎ ለይቶ ስለተናገረ እግዚአብሔር ሶስትነት ያለው መሆኑን በግልጽ ያስረዳል ።
የእግዚአብሔር ሶስትነት ፤ እግዚአብሔር ፤ በስም ፤ በግብር ፤ በአካል ፤ ሶስት ነው ።
የስም ሶስትነት
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በመባል ነው ። “ሂዱና በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቋቸው” ማቴ ፳፰ ፥ ፲፱ ። የአብ ፍቅር ፤ የወልድ ፀጋ ፤ የመንፈስ ቅዱስ ኅብረት ፤ የሚለው ቃል ሶስትነቱን በግልጽ ያስረዳል ። 2ቆሮ 13 ፥ 14 ።
ስሙ (የወልድ) ፤ የአባቱ ስም ፤ የመንፈስ ቅዱስ ስም ፤ የተጻፈባቸው ። ራዕ 14 ፥ 1 ። ከላይ የተገለጹት የእግዚአብሔርን የስም ሶስትነት ያስረዳሉ ።
አብ ፤ በራሱ ሥም አብ ይባላል እንጅ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አይባልም ። ሶስቱም በየስማቸው ይጠራሉ ። ሃይ አበው ምዕ 11. ክፍል 1 ፡ 7 ።
“ሥላሴ” ማለት ሶስትነት ማለት ሲሆን ፤ የአብ የወልድና የመንፈስ ቅዱስ የሶስትነት ጥቅል ስም ነው ። “ሥላሴ” በምን ልበት ጊዜ አብ ፤ ወልድ ፤ መንፈስ ቅዱስ ፤ ማለታችን ነው ።
የግብር ሶስትነት
ግብር ሥራ ማለት ሲሆን ፦ በዚህ ክፍለ ትምህርት የእግዚአብሔርን የግብር ሶስትነት (አብ አባት ፣ ወልድ ልጅ ፤ መንፈስ ቅዱስ ሰራጺ መሆናቸውን) እናያለን ።
አብ ማለት አባት (ወልድን የወለደ) ። ማቴ 3 ፥ 17 ። አስራጺ መንፈስ ቅዱስን ያሰረጸ (ያስገኘ) ። ዮሐ 15 ፥ 26 ።
ወልድ ፤ ተወላዲ (ከአብ የተወለደ) ። ሉቃ 1 ፥ 35 ።
መንፈስ ቅዱስ ማለት ፤ ሰራጺ (ከአብ የሰረጸ) ። ዮሐ ፲፭ ፥ 26 ። ማለት ነው ።
የግብር ሶስነቱ የስሙን ሶስትነት ይገልጻል ። አብ አባት ፣ ወልድ ልጅ ፣ መንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ (ሕይወት)፣ በማለት ። ይህ ማለት ግን አብ አባትና አስገኝ ፣ ስለተባለ ከአብና ከወልድ አይቀድምም አይበልጥም ፤ ወልድም ከአብ አያንስም ፤ ከመ ንፈስ ቅዱስ አያንስም ፤ መንፈስ ቅዱስም ከአብ ከወልድ አያንስም ። ሁሉም እኩል በአንድነትና በሶስትነት ይመሰገናሉ ።
የአካል ሶስትነት
ለአብ ፣ ለወልድ ፣ ለመንፈሰ ቅዱስ ለየራሳቸው ፍፁም (ሙሉ) ገጽ ፣ ፍፁም መልክ ፣ ፍፁም አካል ፣ አላቸው ።
ገጽ ፊት ማለት ሲሆን ፣ ከአንገታችን በላይ የሚታዩት የሰውነት ክፍሎቻችንን ዓይን ፣ ጆሮ…. የመሳሰሉትን ያጠቃልላል ።
መልክ በእያንዳንዳቸው የሰውነታችን ክፍሎች (እግር ፣ እጅ ፣ ራስ ፣ ፀጉር ፣ ዓይን ፣ ጆሮ…..) ተብለው ሲቆጠሩ ነው ።
አካል በአጠቃላይ ሙሉው የሰውነታችን ክፍል ነው ። የፍጡራን አካል የሚታይ ፣ የሚዳሰስ ፣ የሚመጠን ፤ የሚወሰን ፣ ሲሆን የሥላሴ አካል ግን ፤ የማይታይ ፣ በእጅ የማይዳሰስ ፣ በቦታ የማይወሰን ፣ በሁሉም ሙሉ ነው ። መዝ 138 ፥ 7 ።
የእግዚአብሔር የአካል ሶስትነት ። በማቴ 3 ፥ 16 ። እንደተገለጠው አብ በደመና ፣ ወልድ በለበሰው ሥጋ ፣ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል በመሆን በግልጽ ታይቷል ። በሌላም በኩል ለአብርሐም በሶስት ሰዎች አምሳል የተገለጠለት ፣ በአካል ሶስት መሆኑን ሲያስረዳው ነው ። የሥላሴ ሶስትነት ከሰዎች የሂሳብ ቀመር ልዩ ስለሆነ (ቅድስት ሥላሴ) ልዩ ሶስትነት ይባላል ። በሂሳብ ህግ አንድ ሲሆን ሶስት…. የሚሆን ነገር የለምና ። የየራሳቸው የሶስትነት ፣ ሥም ፣ ግብር ፣ አካል ፣ አላቸው ።
የእግዚአብሔር አንድነት
የእግዚአብሔር ሶስትነት በሶስት ነገሮች በስም ፣ በግብር ፣ በአካል ፣ ብቻ ሲሆን በሌላው ሁሉ ለምሳሌ በባህርይ በህልውና ዮሐ 14 ፥ 8 ። በፈቃድ ፣ በሥልጣን ፣ በመፍጠር… ፣ አንድ ነው ። ለአብ ለወልድና ለመንፈስ ቅዱስ በተለያየሥራና ደረጃ ተጽፎ ብናገኝም የስማቸውን የግብራቸውንና የአካላቸውን ሶስትነት ለመግለጽ እንጅ በአንዱ ሥራ ሁሉም አሉበት ። ዓለምን ፈጥሮ እየገዛ ያለ ፣ ሰው ሆኖ ዓለምን ያዳነ ፣ አምላክ አንድ ብቻ ነው ። ኤፌ 4 ፥ 5 ።

ኩነት (ከዊን)

ኩነት ወይም ከዊን ማለት ሁኔታ ወይም መሆን ማለት ሲሆን ፣ ይህም በሰው ነፍስ ምሳሌ ይገለጻል ። ነፍስ አንዲት ስትሆን ሶስት ባህርያት (ኩነታት) አሏት ፤ እነሱም ፤ ልብ (ማሰብ) ፤ ቃል (መናገር) ፤ እስትንፋስ (ሕይወት) ናቸው ። ከሶስቱ ባህር ያት አንዱ ከተጓደለ ነፍስ የሚለውን ስም ልታገኝ አትችልም ።
የእግዚአብሔር ሶስትነት በሰው ነፍስ ምሳሌ ሆኖ ቀርቧል ። ይኸውም አብ በልብ (ማሰብ) ፣ ወልድ በቃል (መናገር) ፣ መን ፈስ ቅዱስ በእስትፋስ (ሕይወት) ሲሆን አብ ለራሱ ልብ ሆኖ ለወልድና ለመንፈስ ቅዱስ ልባቸው ነው ። ወልድም ለራሱ ቃል ሆኖ ለአብና ለመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ነው ። መንፈስ ቅዱስም ለራሱ ሕይወት ሆኖ ለአብና ለወልድ ሕይወታቸው ነው ። በእግዚአብሔርነቱ ፤ ልብ ፣ ቃል ፣ ሕይወት አለ ። ነፍስ ሶስት ባህርያት ቢኖሯትም አንድ እንደምትባል እግዚአብሔርም ሶስት ስም ፤ ሶስት ግብር ፤ ሶስት አካል ፤ ቢኖረውም አንድ አምላክ እንጅ ሶስት አማልክት አይባልም ። ዘዳ 6 ፥፬ ። ሚል 2 ፥ 10 ።
የእግዚአብሔርን አንድነትና ሶስትነት ለማስረዳት የቀረቡ ምሳሌዎች

ፀሀይ

አካል (መጠን) ብርሃን ሙቀት አላት ። በአካሏ አብ ፣ በብርሃኗ ወልድ ፣ በሙቀቷ መንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ሆነው ቀርበዋል ። ፀሀይ ሶስት ሁኔታዎች ሲኖሯት አንድ እንደሆነች እግዚአብሔርም አንድ ሲሆን ሶስት ፤ ሶስት ሲሆን አንድ አምላክ ነው ።

ውሃ

ይዘት(ስፋት) ፣ እርጥበት ፣ ቅዝቃዜ አለው ። በይዘቱ (በስፋቱ) አብ ፣ በእርጥበቱ ወልድ ፣ በቅዝቃዜው መንፈስ ቅዱስ ይመሰላሉ ። ውሃ አንድ እንደሆነ እግዚአብሔርም አንድ ሲሆን ሶስት ፤ ሶስት ሲሆን አንድ አምላክ ነው ።
ሌሎቹም በምሳሌነት የሚቀርቡ ፍጥረታት አሉ ። ነገር ግን በምሳሌነታቸው ለማስተማር እንጅ የአምላክን ባህርይ የፍጡር ባህርይ ሊያስረዳ አይችልም ።
የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

Lየኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት

የኃይማኖት ትምህርት




Reserve 

Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 

Reserve

Reserve

Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 

Reserve

Reserve

Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Reserve 
Share by: